06/08/2026
በአንጋጫ ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ በተለምዶ ካቢኔ ሰፈር ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ በግምት ከ7ወር በላይ የሆነት ህጻን አንጋጫ ከተማ ተገኝታለች ።
በከተማ አስተዳደር በ28/11/2018 ዓ/ም ዕለተ ማክሰኞ ከቀኑ 9:30 ገደማ ተጥላ የተገኘች ህጻን ከአከባቢው ሕዝብ በደረሰ ጥቆማ መሠረት የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ክትትል አድርጎ ሕኗን ከተጣለችበት በማንሰት ወደ አንጋጫ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በመዉሰድ ተገቢውን እንክብካቤ እንድታገኝ አድርጓል ።
በመሆኑም ለህጻኗ ተገቢውን እንክብካቤ እንድታገኝ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ የህጻኗን ወላጅ ወይም ቤተሰብ እየተጠባበቀ መሆኑን በመግለጽ እስካሁን ባሉ ቀናት የሕፀኗ ወላጅ/ቤተሰብ ያልተገኘ በመሆኑ በከተማ አስተዳደሩ እጅ በጥሩ እንክብካቤ ለይ ትገኛለች።
ይሁን እንጂ የከተማ አስተዳደሩ ሕጻኗን ከዝህ በላይ በራሱ እጅ ለማቆየት ሕግ ስለማይፈቅድ ይህ ማስታወቅያ ከተለጠፈበት ከዛሬ ቀን ጀምሮ በ 72 ሰዓት ዉስጥ ወላጅ/ ቤተሰብ ሕጋዊ መረጃ በመያዝ የአንጋጫ ከተማ አስ/ር ፖሊስ ጽ/ቤት ድረስ እንድቀርብ እያሳወቅን ሕጋዊ ወላጅ የማይገኝ ከሆነበአድሱ ቤተሰብ ህግ መሠረት ከምመለከታቸዉ አካላት ጋር በመቀናጀት ህጻኗን መንከባከብ ለሚችል አካል በፍርድ ቤት በማስወሰን ለመስጠት የሚገደድ መሆኑን ከወድሁ እንገልፃለን ።