Fune Media

Fune Media Ethiopia

ታማኝ አባት ኢየሱስ ነዉ! በኢየሱስ ያመነ ሕይወትን እንጂ ሞትን አያይም። በብርሐን እንጂ በጨለማ አይኖርም። ወደ ምሕረት እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም! ኢየሱስ ነፍስን ከሞት ከወጥመድ የሚያወጣ...
15/07/2026

ታማኝ አባት ኢየሱስ ነዉ!

በኢየሱስ ያመነ ሕይወትን እንጂ ሞትን አያይም። በብርሐን እንጂ በጨለማ አይኖርም። ወደ ምሕረት እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም! ኢየሱስ ነፍስን ከሞት ከወጥመድ የሚያወጣ ያመነችበትን ነፍስ የማያሳፍር ታማኝ አባት፤ ብቸኛ አዳኝ ነው!!

በጣም የሚገርም የዝንቧ ታሪክ🤔😂ከአንድ Facebook ገጽ የተቀዳ አስተማሪ ፅሁፍ ነው 👇አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረደት ክንፎቿ ዝለው፣ ሰውነቷ ተንቀጥቅጦ የምታርፍበት ስትፈልግ... በ...
12/07/2026

በጣም የሚገርም የዝንቧ ታሪክ🤔😂

ከአንድ Facebook ገጽ የተቀዳ አስተማሪ ፅሁፍ ነው 👇

አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረደት ክንፎቿ ዝለው፣ ሰውነቷ ተንቀጥቅጦ የምታርፍበት ስትፈልግ... በአንድ ግዙፍና ጉልበታም በሬ ቀንድ ላይ አረፈች። እዚያው ተደግፋ፣ በጠራራው ፀሐይ እየተሞቀች ረዥም ሰዓታት አሳለፈች።

ብርዱ ለቆላት፣ ነፍስ ሲዘራባትና ለመብረር ስትዘጋጅ ግን ራሷን ዝቅ አድርጋ ማየት አልፈለገችም። ወደ በሬው ጆሮ ጠጋ አለችና በትዕቢት

"አዝናለሁ በሬ ሆይ... እንግዲህ መሄዴ ነው፤ ብቻህን ልተውህ ነው" አለችው።

በሬው ግን ምንም ሳይደነግጥ፣ ቀና ብሎ እንኳ ሳያያት በረዥሙ ተነፈሰና እንዲህ አላት፦

"ስታርፊ አልተሰማኝም፤ ስትነሺም የሚሰማኝ አይመስለኝም!"

በሕይወታችን ጉዞ ውስጥ እንደዚች ዝንብ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። መኖራቸው ቅንጣት ታህል የማይጠቅም፣ መሄዳቸውም ለአንዳች ነገር የማይጎዳ ሆነው ሳለ... ራሳቸውን ግን የዓለም ማዕከል አድርገው የሚቆጥሩ (Main Character Syndrome ያለባቸው) ሞልተዋል።

ሲመጡ፦ ባዶነታቸውን ልንሸፍንላቸው እንደተሸከምናቸው አይረዱም።

ሲኖሩ፦ መገኘታቸው ለሕይወታችን ምንም ዓይነት ትርጉም አይጨምርም።

ሊሄዱ ሲሉ ግን፦ ዓለም የተደፋችብን ይመስል "እሄዳለሁ!" እያሉ ሊያስፈራሩን ይሞክራሉ።

የእርስዎን ክብደት፣ ዋጋና ማንነት ለማያውቁ ሰዎች "እሄዳለሁ" የሚለው ማስፈራሪያ በጭንቀት አይቀበሉት። መሄዳቸው ለእናንተ የሸክም መቅለል፣ የነፃነት መታደስ ነው።

ሕይወታችሁን ሳያደምቁ "እሄዳለሁ" ብለው ለሚያስፈራሯችሁ ሰዎች ሁሉ... በሬው የሰጠውን አይነት ቀዝቃዛና ጥቆማዊ ምላሽ ስጡና እረፉ! መውጣት ለፈለገ መንገድ ልቀቁለት፤ ምክንያቱም የእነሱ መሄድ የእናንተን ክብደት አይቀንሰውም!

Fune Media

እግዚአብሔር  ስረዳ ከሰማያት  ወርዶ፦"ከሰሞኑ በተለቀቀ አንድ ምስል ምክኒያት ይህች ታዳጊ የአብዛኛውን ማህበረሰብ እና የብዙ ድርጅቶችን ቀልብ ገዝታለች፣ በዚህ በጎ አጋጣሚ ህይወቷን መቀየር...
10/07/2026

እግዚአብሔር ስረዳ ከሰማያት ወርዶ፦
"ከሰሞኑ በተለቀቀ አንድ ምስል ምክኒያት ይህች ታዳጊ የአብዛኛውን ማህበረሰብ እና የብዙ ድርጅቶችን ቀልብ ገዝታለች፣ በዚህ በጎ አጋጣሚ ህይወቷን መቀየር እንድትችል፣ ሀገሯን በዓለም እንድታስጠራ እኛም የአቅማችንን ለማድረግ ከትውልድ ቦታዋ ከቤተሰቦቿ ጋር በመነጋገር ወደ አዲስ አበባ ይዘናት መተናል""" ማስተር አብነት ከበደ እና ቲክታከር ሀያት ያስን ሀዩቲ

ቴዲ 100 ሺህ ብር ከፍሎ ከእስር አስፈታኝ!❤️🙏የታላቁ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) "ኢቶሪካ" አልበም ግራፊክስ ዲዛይነር የሆነው ወጣት ዳዊት ሰለሞን፣ ለኪነጥበብ አባቱ ለቴዲ አ...
08/07/2026

ቴዲ 100 ሺህ ብር ከፍሎ ከእስር አስፈታኝ!❤️🙏

የታላቁ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) "ኢቶሪካ" አልበም ግራፊክስ ዲዛይነር የሆነው ወጣት ዳዊት ሰለሞን፣ ለኪነጥበብ አባቱ ለቴዲ አፍሮ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።

የ23 ዓመቱ ወጣት ዳዊት፣ ከወራት በፊት ጓደኞቹ ጋር በሄደበት አጋጣሚ በፖሊስ ተይዞ በእስር መቆየቱ ይታወሳል ።

ዳዊት በአቃቢ ህግ ክስ ተመስርቶበት ፍርዱን ሲከታተል ቆይቶ በ100 ሺህ ብር ዋስትና እንዲለቀቅ ፍርድቤት ወስኗል።

የቴዲ አፍሮ ግራፊክስ ዲዛይነር ዳዊት የተጠየቀውን ገንዘብ በመክፈል በዋስ መለቀቁን ገልጾ፤ ቴዲ አፍሮ ዳዊት ጨምሮ አብረውት የታሰሩትን ተጠርጣሪዎችን የዋስትና ገንዘብ ከፍሎ ከእስር እንዲወጡ ማድረጉን ተናግሯል።

ወጣቱ ዳዊት የተጠየቀውን የዋስትና ገንዘብ ክፍያ ቴዲ አፍሮ በመክፈሉ ልባዊ ምስጋናውን ገልጾ፤"ማኔ ቴቄል ፋሬስ"በማለት የእግዚአብሔር ፍርድን የሚያመለከት መልዕክት አጋርቷል። ትርጉሙም “ተቆጥሯል፣ ተመዝኗል፣ ተከፍሏል” የሚለውን ትርጉም ይይዛል።

የግራፊክስ ባለሙያው ዳዊት ከምስጋና ባሻገር ለንጉሱ ቴዲ አፍሮ ለ50ኛ የልደት በዓሉ መልካም ምኞቱን ገልጿል።

Vዳዊት ሰለሞን

ከሀደሮ ምድር የተገኘው ድንቅ ውበት። የዚህችን ታዳጊ ህይወት እስከመጨረሻው ለመለወጥ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። እኔም ከከምባታ ሀላፊነቱን ወስጄ በብሩክ ኒውስ አማካኝነት እየመጡላት...
07/07/2026

ከሀደሮ ምድር የተገኘው ድንቅ ውበት። የዚህችን ታዳጊ ህይወት እስከመጨረሻው ለመለወጥ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። እኔም ከከምባታ ሀላፊነቱን ወስጄ በብሩክ ኒውስ አማካኝነት እየመጡላት ያሉትን በርካታ ስራዎች እንድተሰራ ለማድረግ ስራ ጀምረናል። ይህችን ታዳጊ አሁንም አግዟት፣ ከብሩክ ኒውስ ጋር ሆነን የደረስንበትን እናሳውቃቹሀለን።
Master Abinet Kebede

 በባምባሲ ከተማ አስተዳደር በ02 ቀበሌ ልዩ ስሙ  የሙስሊሞች መካነ መቃብር አካባቢ በትላንትናው እለት ማለትም ሰኔ 26/2018 ዓ.ም የተወለደች የአንድ ቀን ሕፃን በአሳዛኝ ሁኔታ ተጥላ የ...
04/07/2026



በባምባሲ ከተማ አስተዳደር በ02 ቀበሌ ልዩ ስሙ የሙስሊሞች መካነ መቃብር አካባቢ በትላንትናው እለት ማለትም ሰኔ 26/2018 ዓ.ም የተወለደች የአንድ ቀን ሕፃን በአሳዛኝ ሁኔታ ተጥላ የተገኘች ሲሆን፣

ፖሊስ ከማህበረሰቡ ጋር በመተባበር ከተጣለችበት የቀብር ቦታ በማንሳትና የሕክምና እርዳት እንድታገኝ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ የጨቅላዋ ሕፃን ተገቢው የሕግ ሂደቶች ተሟልቶ መፍትሔ እስከሚሰጥ ድረስ በከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ የሴቶችና ህፃናት አማካኝነት እንክብካቤ እየተደረገላት ይገኛል ።

ማህበረሰቡም በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ አስነዋሪ ድርጊቶችን በጽኑ ሊያወግዝና ከጅምሩ መነሻ ምክኒያቶችን በጋራ መከላከል እንደሚገባ ለማሳሰብ እንወዳለን ‼️

የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የመከላከያ ኃይል በርካታ ንግዶች ከተዘረፉ በኋላ በደርባን በስተምዕራብ ክሌርሞንት ወደሚገኘው ክዋዳቤካ ተሰማርቷል። ቢያንስ ሁለት ሱፐርማርኬቶች እና የጥርስ ህክምና ተ...
01/07/2026

የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የመከላከያ ኃይል በርካታ ንግዶች ከተዘረፉ በኋላ በደርባን በስተምዕራብ ክሌርሞንት ወደሚገኘው ክዋዳቤካ ተሰማርቷል። ቢያንስ ሁለት ሱፐርማርኬቶች እና የጥርስ ህክምና ተቋማት በአንድ ሌሊት ተዘርፈዋል። በተከሰቱት ክስተቶች እቃዎች እና መሳሪያዎች ተሰርቀዋል።

መረጀው ከ SABC News

ሠላም ለእናንተ ይሁን የዚህ ገጽ ተከታታዮች በተረፈ ደቡብ አፍሪካ ለምትኖሩ ወንድም እህቶቻችን ትልቁ መፍትሔ የተጀመረውን ፀሎት ማጠናከር ፣ በጥበብ መመላለስ፣አንድነትን ማጠናከር ፣የመረጃ ስ...
01/07/2026

ሠላም ለእናንተ ይሁን የዚህ ገጽ ተከታታዮች በተረፈ ደቡብ አፍሪካ ለምትኖሩ ወንድም እህቶቻችን ትልቁ መፍትሔ የተጀመረውን ፀሎት ማጠናከር ፣ በጥበብ መመላለስ፣አንድነትን ማጠናከር ፣የመረጃ ስርጭት እና ግኝት ላይ በጥንቃቄ ማድረግ ፣የሀገሩን ዜጎች ከሚነኩ መልዕክቶች በፍጹም መቆጠብ፣በተለይ በሆነ ጥላቻ ወንድም ወንድሙን ከሚጎዱ ከማንኛውም ድርጊት ራስንና ሌሎችን ነፃ ማድረግ ፣በአጠቃላይ እግዚአብሔር በባህር ውስጥ መንገድ አለው ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ይህ ጊዜም ያልፋል ነጌ በጌታ መልካም ይሆናል እርሱ ሌላም ሀገር አለው በጣም አትጨነቁ እግዚአብሔር ነገር ሁሉ ታማኝ እና ፀድቅ ነው እርሱ ሁሉንም ያውቃል ጌታ ጠልቃ ገብቶ ንቅናቄውን ለመልካም እንዲያደርግ (እንድቀይር)ሁሌም መጸለይ ያስፈልጋል ወገኖቼ

ሰላም ጤና ይስጥልን በደቡብ አፍሪካ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያን በያላችሁበት በዘጠኙም ክልል ሰላማችሁ ይብዛ🙏🕊   #ጁን 30 ለሚደረገው ሰልፍ መንግስት "በቂ ዝግጅት አድርጌያ...
28/06/2026

ሰላም ጤና ይስጥልን በደቡብ አፍሪካ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያን በያላችሁበት በዘጠኙም ክልል ሰላማችሁ ይብዛ🙏🕊

#ጁን 30 ለሚደረገው ሰልፍ መንግስት "በቂ ዝግጅት አድርጌያለሁ" ቢልም፣ እኛ ግን ከምንም በላይ ለራሳችን ደህንነት ቅድሚያ እንስጥ!
ከተቻለ በቤታችን እንሁን።
ካልሆነ ደግሞ ፍጹም ሰላማዊ በሆኑ አካባቢዎች ላይ ብቻ እንቀሳቀስ።
የትኛውንም የመኖሪያ ፍቃዳችንን መያዛችንን እርግጠኛ እንሁን።

​ፈጣሪ ወገኖቻችንን ሁሉ ይጠብቅ!

እኔ እንደ ሰው ልጅ ውሾችን መግደል እቃወማለሁ!! 🙅‍♀️🙅‍♂️🐩🐕 ውሻ እንደማንኛውም እንስሳት ነፍስ ያለው የቤት እንስሳ ነው ።አንድ ውሻ ሰውን ነክሶ ሰው ሞተ ብላህ ሁሉንም ውሾች መግደል...
27/06/2026

እኔ እንደ ሰው ልጅ ውሾችን መግደል እቃወማለሁ!! 🙅‍♀️🙅‍♂️

🐩🐕 ውሻ እንደማንኛውም እንስሳት ነፍስ ያለው የቤት እንስሳ ነው ።

አንድ ውሻ ሰውን ነክሶ ሰው ሞተ ብላህ ሁሉንም ውሾች መግደል ተገቢ ነው ወይ ⁉️
ውሾችን ከመግደል መፍትሔ መፈለግ አይበጅም ወይ ⁉️

🐂🐃 አንድ በሬ ወይም ደግሞ አንድ ላም ሰውን ወግተው ሰው ሞተ ስባል ያ በሬ ወይም ላም ይገደል ብለህ ትዕዛዝ ታወጣለህ ወይ⁉️ይመስለኛል መልስህ በፍጹም አይሆንም ነው ምክንያቱም ነፍስ ስለሆነ 🤔
ታዲያ የውሻችስ ነፍስ አይደለም ወይ እነሱስ ስገደሉ እንዴት ይሆናሉ አይሰቀዩም ወይ በዛን ሰዓት ቢትሆን ምን ይሰማሃል ⁉️

ጥያቄው ለማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ ለሆነችው ሆሳዕና ከተማ አመራሮችና ለሕግ አውጪዎች ⁉️

በጣም ያሳዝናል 😭😭

ለውሾች ክትባት መስጠትና ማሰር እንጂ መገደል መፍትሔ አይሆንም ።🙅‍♂️

Fune Media

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fune Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category