Ethiopian Malda News View

Ethiopian Malda News View የሀሳብ የበላይነት ያሸንፋል። ኢትዮጵያ ያይኔ ማረፊያ። ������

በሶማሊያ የሁለቱ የኢትዮጵያ ወታደሮች የፈጸሙት ጀብዱ በአራት ተከታታይ  ክፍል በመክፈል እንደሚከተለው ይቀርባል ። ታሪኩ የሚጀምረው በአንድ ጨለማ ሌሊት በሶማሊያ ድንበር አቅራቢያ ነው።ክፍል...
22/12/2025

በሶማሊያ የሁለቱ የኢትዮጵያ ወታደሮች የፈጸሙት ጀብዱ በአራት ተከታታይ ክፍል በመክፈል እንደሚከተለው ይቀርባል ።
ታሪኩ የሚጀምረው በአንድ ጨለማ ሌሊት በሶማሊያ ድንበር አቅራቢያ ነው።

ክፍል ፩ (1) ፦ ጥቁሩ ሌሊት

​በደቡባዊ ሶማሊያ በሂርሸበሌ ክልል የሚገኘው "የሃልገን " በረሃ እንደ ምጣድ ይጋላል። ፀሐይ ስትጠልቅ የነበረው ቀይ ወጋገን አሁን ቦታውን ለጭለማ ሰጥቷል። ጭለማው ግን ሰላም አልነበረም፤ ይልቁንም የሞት ሽታን አርግዟል።
​ሻምበል ካሳሁን በአሸዋማው ጉድጓድ ውስጥ ተደፍቶ በሌሊት መመልከቻ መነፅሩ አካባቢውን ይቃኛል። አቧራ የለበሰው የደንብ ልብሱ ከበረሃው አፈር ጋር ተዋህዷል። ከጎኑ መቶ አለቃ አማኑኤል የ"ድራጉኖቭ" ስናይፐር ጠመንጃውን ደግኖ ትንፋሹን ዋጥ አድርጓል።
​"አይታዩም ሻምበል..." አለ አማኑኤል በሹክሹክታ። ድምፁ ውስጥ የንዴትና የጭንቀት ስሜት ይንፀባረቃል።
​ካሳሁን አልመለሰለትም። የልቡ ትርታ ግን እንደ ከበሮ ይደልቃል። ከአንድ ሰዓት በፊት ከአልሸባብ የደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት ካምፓቸውን አናውጦታል። በዚያ ግርግር መሃል ነበር በድንገት የሬዲዮ መገናኛ ባለሙያው ፲/አለቃ ዮናስ በጠላት ታግተቶ የተወሰደው። ዮናስ የቡድኑ "ጆሮ" ብቻ አልነበረም፤ ለካሳሁን እንደ ታናሽ ወንድም፣ ለአማኑኤል ደግሞ የልጅነት ጓደኛው ነበር።
​"ወደ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ ነው የወሰዱት፣" አለ ካሳሁን በመጨረሻ። መነፅሩን አውልቆ አይኑን አሻሸ። "ቆይ ቆይ... ያንን ተመልከት!"
​በሩቅ፣ ከ ተራራ ስር አንዲት ደብዛዛ ብርሃን ብልጭ ብላ ጠፋች። የሞተር ድምፅ በለሆሳስ ይሰማል። የአልሸባብ ታጣቂዎች ታጋቹን ይዘው ወደ ምሽጋቸው እየገቡ እንደሆነ ግልጽ ነው።
​"ሻምበል፣ ትዕዛዝ አንጠብቅም?" ጠየቀ አማኑኤል፤ ጣቱ የጠመንጃውን ምላጭ እየዳሰሰ።
​ካሳሁን ወደ ሰማይ አየ። ከዋክብቱ በበረሃው ሰማይ ላይ ደምቀው ይታያሉ። "ከመቀመጫችን ትዕዛዝ እስኪመጣ ዮናስን ድንበር ያሻግሩታል። አንዴ 'ጂልብ' ከገቡ ደግሞ መልሰን አናገኘውም።"
​"ታዲያ ምን እናድርግ?"
​ካሳሁን ቀና ብሎ አማኑኤልን በአይኑ ኩራት ተመለከተው። "እኛ የምንሄደው ለጦርነት ሳይሆን ለነፍስ አድን ነው። ሬዲዮህን አጥፋው። ከአሁን በኋላ የምንመራው በልባችን ትርታ ብቻ ነው።"
​አማኑኤል ፈገግ አለ። ያ የሞትና የህይወት ፈገግታ። "ታጥቄያለሁ ሻምበል!"
​ሁለቱ ጀግኖች አፈሙዛቸውን ወደ ጨለማው አቅጣጫ አዙረው ከአሸዋው ጉድጓድ ወጡ። ከኋላቸው ያለው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ሰፈር እየራቀ ሄደ። በፊታቸው ያለው ግን የማይታወቅ አደጋ፣ የጠላት ምሽግ እና የጓደኛቸው ህይወት ነው።
​በዚያ ጥቁር ሌሊት፣ ሁለት ወታደሮች የጓደኝነታቸውን ቃል ኪዳን በደማቸው ሊያትሙ ከአባቶቻቸው የወረሱትን አይበገሬነት ለመድገም ጓዳቸው ወደተወሰደበት አቅጣጫ ጉዞ ጀመሩ።
ክፍል ሁለት ይቀጥላል.....✍️

@በእንዳልክ ሳለሁ ተፈራ

 #ፍትህ
17/08/2024

#ፍትህ

31/03/2024

97?

😭😭😭አባቱ ና የእንጀራ እናቱ ደብድበው ገደሉት::የ 7 ዓመት ህፃን ልጅ በመደብደብ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረጉ ወላጅ አባት እና የእንጀራ እናት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጠራባቸው ይገ...
15/11/2023

😭😭😭

አባቱ ና የእንጀራ እናቱ ደብድበው ገደሉት::

የ 7 ዓመት ህፃን ልጅ በመደብደብ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረጉ ወላጅ አባት እና የእንጀራ እናት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጠራባቸው ይገኛል::

በእሱ ፈቃድ ታምራት የተባለው የ7 ዓመት ህፃን የተወለደው በእናቱ እና በወላጅ አባቱ መካከል በተፈጠረ ጊዜያዊ የፍቅር ግንኙነት ነበር፡፡

ወላጅ እናት ህፃኑን ከወለደች በኋላ ያለ ወላጅ አባቱ ድጋፍ እና እርዳታ ለ6 ዓመት ከወራት ያህል በብዙ ፈተና ውስጥ ሆና ብቻዋን እየኖረች አሳድጋዋለች፡፡

ነገር ግን ኑሮ እየከበዳት ሲመጣ ልጇም አብሯት እንዳይጎሳቆል በማሰብ ሃምሌ 18 ቀን 2015 ዓ/ም ለወላጅ አባቱ አስረክባ እሷ ወደ ጎዳና ኑሮ ወጣች፡፡

ይሁን እንጂ ህፃን በእሱ ፈቃድ ሌላ ሚስት አግብቶ ወደሚኖረው አባቱ የተሻለ ህይወት እንዲገጥመው ታስቦ ቢመጣም ነገሩ የሆነው የተገላቢጦሽ ነው፡፡

በወላጅ አባቱም ሆነ በእንጀራ እናቱ በየጊዜው ድብደባ ይደርስበታል፡፡ በብረት ሰንሰለት እየታሰረ መከራውን ያያል፡፡ በደረሰበት የስነ ልቦና ቀውስ ሰገራውን መቆጣጠር የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሶ እንኳ ድብደባው አልቀረለትም፡፡

ድንገት የሚያመልጠውን ሰገራ እና ምግብ በልቶ በሆዱ አልረጋ ብሎት የሚያስመልሰውን በምላሱ እንዲልስ እስከማድረግ የደረሰ ግፍ ሲፈፀምበት ቆይቷል፡፡

በጥቅምት ወር 2016 ዓ/ም ህፃን በእሱ ፈቃድ በደረሰበት ድብደባ ራሱን ስቶ ሲወድቅ ወላጅ አባቱ እና የእንጀራ እናቱ አፋፍሰው ወደ ጤና ጣቢያ ይዘውት ይሄዳሉ፡፡

ጤና ጣቢያ የደረሱት ግን ህይወቱ ካለፈ በኋላ ነበር፡፡ የህፃኑ መሞት በጤና ባለሙያዎቹ ሲነገራቸው አባቱ እና የእንጀራ እናቱ የአስክሬን ሳጥን ገዝተን እንምጣ ብለው በዚያው ቀርተዋል፡፡

ስለተፈፀመው ወንጀል አቤቱታ የደረሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ የሰው መግደል ወንጀል ምርመራ ክፍል ተጠርጣሪዎቹን ተከታትሎ በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ ይገኛል፡፡

የህፃን በእሱፈቃድ አስክሬን በጎረቤት እና በአካባቢው ነዋሪዎች ትብብር በቀጨኔ መድሃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል፡፡

Via AAP

😭😭😭

🌴🌴🌴

ስንቱን በልተው የስንቱን ለጋ እድሜ ቀምተው የስንቱን ወላጆች ልብ አድመተው የስንቱን ህልም በቀብር ላይ እንዲያልፍ አድርገው እነሱ ስንት አመት እንደሚኖሩ አብረን እናያዋለን። ሰላማዊዮን ህዝ...
03/06/2023

ስንቱን በልተው የስንቱን ለጋ እድሜ ቀምተው የስንቱን ወላጆች ልብ አድመተው የስንቱን ህልም በቀብር ላይ እንዲያልፍ አድርገው እነሱ ስንት አመት እንደሚኖሩ አብረን እናያዋለን። ሰላማዊዮን ህዝብ ነው በግድ ጦርነት ካልገጠማችሁኝ ብለው እራሳቸው ነገር የፈለጉት። ጦርነት ለፈለገ ግን ወደ ጉጅ ወይም ወደ ምዕራብ ወለጋ ብቅ ቢል አፍንጫቸው ስር ሽምቅ ተዋጊ አለላቸው ነበር። በድሀ ላይ ሁሉም ጀግና ነው። ድሀን ድሮም የተሸነፈ ነው። አንደኛ ድሀ ነው። ሁለተኛ ደካማ ነው። ሦስተኛ ምንም ቢደረግ ምን ያመጣል? ድሀን ብትገለው ብታፈናቅለው ብትዘርፈው ብትሰድበው ምንም አያመጣም። የዚህ መንግስት ትልቁ ጀግንነት እመሀል ከተማ ውስጥ ያለን ድሀ ማሸነፍ ነው። ለዚህ ነው በድሀ ጠንካራ ሆኖ የታየው። በገዛ እጃቸው ፍፅም ከዕውቀት ነፃ በሆነ የአስተዳደራዊ ፖሊሳቸው አለም እየሳቀባቸው ዞረው ምንም ብቃት የለለውን የስለላና የፖሊስ ሀይላቸው ጠንካራ እንዲመስል ሀሰተኛ ዶክመንተሪኢ እየሰሩ ሙድ የሚያዝባቸው።

በዚህ ቅፅፈት ቢሊዮን ዶላር በህገወጥ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ነው። እርግጠኛ ነኝ አሁን በዚህ time ወደጅቡቲ በህገወጥ መንገድ ወርቅ ተጭኖ
እየሄደ ነው። እና የቱ የስለላ ሀይላቸው ነው የሚይዘው የቱ ፖሊሳቸው ነው የሚያድነው.? የለም። ምክኒያቱም በብቃት የተመለመለ ሀይል የላቸውም። በብሄር በአደግዳጊነት የተመለመለ ማዋቅር ነው ያላቸው። አይማሩም እንጅ ልክ እንደዮንቨርቲ ሆነን ሁሉንም ነግረናቸው ነበር።

ለማንኛውም ሟቹ ወንድማችን አንተና የመሰዋት ጓደኞች አብራችሁ ምህረቱን ይስጣችሁ። ለቤተሰቦቻችሁ መፅናናትን እመኛለሁ።

ሱሌማን አብደላ

02/06/2023
ይሄ የምታዩት ጠላትን ተጋድሎ ሀገርን ለማትረፍ በወታደሮች የተከፈለ መስዋዕትነት አይደለም ሙስሊም ወንድሞቼን ለመጨፍጨፍ ያደረጉት ነው ። ግንቦት 25/2015
02/06/2023

ይሄ የምታዩት ጠላትን ተጋድሎ ሀገርን ለማትረፍ በወታደሮች የተከፈለ መስዋዕትነት አይደለም ሙስሊም ወንድሞቼን ለመጨፍጨፍ ያደረጉት ነው ።

ግንቦት 25/2015

___________  !___________                🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹መንጌ ዛሬ 82ኛ አመት የልደት በዓላቸውን እያከበሩ ነው። እንኳን በህይወት ኖረው...
27/05/2023

___________ !___________

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

መንጌ ዛሬ 82ኛ አመት የልደት በዓላቸውን እያከበሩ ነው። እንኳን በህይወት ኖረው ይህቺን ቀን ለማክበር አበቃዎ!

እርስዎ ለአመታት የጮሁለት፣ የታገሉለትን፣ የወተወቱትን አልሰማ ብለን ዛሬ ሃገራችን በከባድ አደጋ ውስጥ ገብታ ይኸው አፋፍ ላይ ቆመናል።

የእርስዎ ውትወታና ጩኸት ከበፊቱ ይበልጥ ጆሯችን ውስጥ እያስተጋባ ያስቸገረን አሁን ነው!

ለማንኛውም መልካም የልደት በዓል እንዲሆንልዎ ልጅዎ እመኝልዎታለሁ።

HAPPY BIRTHDAY MENGE! WE LOVE & RESPECT YOU!

አዲስ አበባ :  ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ  | በአዲስ አበባ ከተማ መገናኛ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሥድሥት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ዛሬ ከምሽቱ 1:12 ሰዓት ገደማ መገ...
20/02/2023

አዲስ አበባ : ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ

| በአዲስ አበባ ከተማ መገናኛ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሥድሥት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

ዛሬ ከምሽቱ 1:12 ሰዓት ገደማ መገናኛ አደባባይ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ተጎጂዎች በአንቡላንስ ወደ ተለያዩ ጤና ተቋማት መወሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

የአደጋው መንስኤና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር እየተጣራ መሆኑንም አቶ ንጋቱ ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም እነሱ ተጨባበጡ ሌላው አጨበጨበ
02/11/2022

በመጨረሻም እነሱ ተጨባበጡ ሌላው አጨበጨበ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Malda News View posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share