06/09/2026
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ የፈጀው ዘመናዊው እና ውብ ተደርጎ የተገነባው ግዙፉ የአስተዳደር ህንፃ በደመቀ መልኩ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ ዝግጁ ሆኗል።
ህንፃው ዘመናዊ የደህንነት ካሜራዎች የተሟሉለትና ዘመናዊ የህንፃ ጥበብ አሟልቶ የተገነባ ባለ 9 ወለል ህንፃ ነው።
የዚህ ህንፃ ግንባታ የጉራጌ ህዝብ የአንድነት፣ የጥንካሬና የልማት አዲስ ምዕራፍ ጅማሮ ማሳያ ነው
ይህ አዲስና ዘመናዊ የአስተዳደር ህንፃ ግንባታ የድንጋይና የኮንክሪት ክምችት ብቻ አይደለም፤ የጉራጌ ህዝብ የማንነት፣ የውበት፣ የትጋትና የታላቅነት መገለጫ አዲስ አሻራ ነው!
የህዝባችን የልማት ተምሳሌትነት፡ የጉራጌ ህዝብ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር በራሱ ጥረትና ላብ ተዓምር መስራት የሚችል፣ "በራሴ እጅ" ባይ ኩሩ ህዝብ ነው። ይህ ህንፃ የዚሁ የማይበገር የስራ ወዳድነት መንፈስ ህያው ምስክር ይሆናል።
ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ፤ ዛሬ የምናስቀምጠው እያንዳንዱ ሳንቲምና የምናፈሰው ጠብታ ላብ ነገ ልጆቻችን በኩራት ቀና ብለው የሚሄዱበትን ታሪክ ይሰራል።
የህንፃው መጠናቀቅ ለዞኑ ማህበረሰብ የሚሰጠውን የመንግስት አገልግሎት በማዘመን የህዝባችንን እንግልት ይቀንሳል፤ ልማትንም ያፋጥናል።
አንድነት ኃይል ነው ከተማው ከገጠሩ፣ በሀገር ውስጥ ያለው በስደት ከሚኖረው ወገኑ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ ካልተረባረበ ይህ ህልም እውን አይሆንም።
ሀገር እና ስራ ወዳዱ የጉራጌ ማህበረሰብ ጀምሮ የመጨረስ ምሳሌም መሆኑን ይህ ግዙፍ ህንፃ ምስክር ነው።