16/01/2026
ነፂ ዛሬ ጥዋት😂💔
ነጻነት ዛሬ ጠዋት ወደ ስራ ሊሄድ እየለባበሰ ነበረ። ህመም ሲሰማው ጓደኛውን ጠርቶት ወደ ICMC ሆስፒታል ሄዱ። መንገድ ላይ እያለም ህመሙ እየባሰበት ነበረ። ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ምሳ ሰዓት ገደማ አረፈ። ፖሊሶች በሆስፒታሉ ተገኝተው ሙያዊ የምርመራ ስራቸውን አከናውነዋል።
አሌልቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅበሩኝ
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በሕይወት እያለ ሲሞት አሌልቱ ጊዮርጊስ ከአያቱ አጠገብ ቀብሩ እንዲፈጸም እንደሚፈልግ ለወዳጆቹ ደጋግሞ ይናገር የነበረ ሲሆን ያለፈው ሳምንትም አሌልቱ ጊዮርጊስ በመሄድ ቤተክርስቲያኒቱን የማሳደስ ስራ ስለማከናወን ከሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቱ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሮ መመለሱ ተሰምቷል።
ኑሮዋን በአሜሪካ ያደረገችው ባለቤቱ እና የልጆቹ እናት እሁድ ጠዋት ከአሜሪካ አዲስ አበባ የምትገባ ሲሆን በዚያው ሰዓት ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
©ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ