26/11/2025
እንኳን ለእምነ ቅድስት
ወለተ ጴጥሮስ ዓመታዊ
በዓል አደረሰን
ሕዳር 17 በዓለ ዕረፍትዋ ነው
"የጻድቃን ዘር ግን ይድናል።"
ምሳሌ 21፤11
ቅድስት እናታችን የነበረችበት ዘመን
ሐይማኖት የጠፋበት የግፍ አእባን የሚወርድበት
እንዲህ እንዳለንበት ዘመን በፈቃዳቸው ያበዱ በዝተው ሐገር የሚታመስበት መስሎ አዳሪ አብሎ መስካሪ የበዛበት ተፈሪ ተከባሪ የጠፋበት ካህናት የሚታረዱበት ዘመነ ሰማእታት ነበር አፄ ሱስንዮስ እምነት ለውጠው የማሉበትን ወንጌል ክድው በካቶሊካውያን ቤተክርስቲያን መከራዋን ያየችበት ወቅት ይህ ሰአት ነው ቅድስት ወለተ ጴጥሮስን ያስገኘ!!!
ንጉሱ በተገኘችበት እንድትገደል ሞት ቢያውጅባትም በጎንደር ከተማ በገመድ እየተጎተተች ስቃይዋን ቢያበዙም ካህናቱም ሕዝቡንም ከማንቃት ከተዋህዶ እንዳያፈገፍጉ ከማትጋት ማንም ያገዳት የለም ኃይለ እግዚአብሔር አልተለያትምና።
በትዳር ኖራ ሶስት ልጆችንም አፍርታለች ግን የአበው መዋረድ የቤተክርስቲያን መንደድ እመር አድርጎ ከቤትዋ አስወጣት በሰሜን ኢትዮጵያ ሐያል ነበልባል ሆና ንጉሱንም ከሐድያኑንም መድረሻ አሳጣች ብዙዎች መከራን ተሰቅቀው እምነት ክደው እንዳይጠፉ እንደውም ሰማዕትነት ክብር እንዳለው በመግለጽ ብዙዎችን ለሰማያዊ ክብር እንዲበቁ ምክንያት ሆነች።
በዋልድባና በሌሎች ገዳማት በርካታ የመንፈስ ቅዱስ ልጆች ነበራት
ምንኩስናን ተቀብላ የ700 መናንያን እናት እመምኔትም ነበረች ሞትን የማትፈራ ገዳማዊት ባህታዊት ቅድስት እምነ ወለተ ጴጥሮስ ።
እናታችን ዛሬም አትለይን በምልጃሽ ታደጊን በእምነት በምግባር እንድንተጋ ጸሎትሽ ይርዳን በቃል ኪዳንዋ ትጠብቀን
ስለ ግፉአን ስዱዳን በጭንቅ በመከራ ላሉ ከእግዚአብሔር ትማልድልን ምልጃ ጸሎቷ ከዘረኝነት ደዌ ከፍቅር ረሐብ ከዝሙት እሳት ከክሕደት አሽክላ ይሰውረን የተግባር ሰው ኹላችንንም ያድርገን
አሜን አሜን አሜን