Alte pictures

Alte pictures Welcome To Our Page. I Like Captures Photo More in Natural Photo. in this page Natural Photos & Othe

በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የ8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው - የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የ8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜት...
23/02/2026

በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የ8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው - የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ

በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የ8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ በተሳለጠ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሐዋሳ ከተማን በጎበኙበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በከተማዋ እየተከናወነ ላለው የኮሪደር ልማት ትልቅ አቅምና መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን ከንቲባው አክለው ተናግረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የተሻለች ሀገርን ለትውልድ የመገንባት አካል መሆናቸውንና በርካታ ከተሞችን እየለወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በ8 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር መንገድ ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት መሠረታዊ የሚባሉ አገልግሎቶችን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ የሚያደርጉ መሠረተ ልማቶችን ያካተተ ነው።

ይህ የልማት ሥራ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል።

የከተማዋን የትራንስፖርት ፍሰት ለማሳለጥና የተሽከርካሪ መጨናነቅን ለመቀነስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የትራፊክ ፍሰትን የሚያቀላጥፉ 5 አዳዲስ የተሽከርካሪ ተርሚናሎች መገንባታቸውን ጠቁመው ከዚህ ቀደም በከተማዋ ያልነበሩ 13 ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያ(ፓርኪንግ) ቦታዎች መገንበታቸውንም ጠቁመዋል፡፡

ሐዋሳ የቱሪስትና የኮንፍረንስ ከተማ መሆኗን ያነሱት ከንቲባው፤ ለጎብኚዎችም ሆነ ለነዋሪዎች ምቹ የሆነ የእግረኛ መንገድ መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ 17 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የእግረኛ መንገድ መገንባቱን ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚሆነው መንገድ እስከ 7 ሜትር የሚደርስ ስፋት ያለውና ለእግር ጉዞ እጅግ ምቹ ሆኖ የተሠራ ነው።

በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ለሐዋሳ ከተማ ትልቅ ልምድና ተሞክሮ መሆኑንም አቶ ጥራቱ ጨምረው ተናግረዋል።

ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በአጭር ጊዜ ገንብቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበትን ይህንኑ ተሞክሮ በመጠቀም በሐዋሳም ሥራዎች በተሳለጠ ሁኔታ ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት ስብሰባ ጀምረናል።This afternoon, we commenced the Prosperity Party’s coun...
19/02/2026

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት ስብሰባ ጀምረናል።

This afternoon, we commenced the Prosperity Party’s council meetings to deliberate on our strategic priorities.

የቱርክዬው "ቶግ" (Togg) የኤሌክትሪክ መኪና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በስጦታ ተበረከተየቱርክዬው ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይብ ኤርዶዋን በኢትዮጵያ እያደረጉት ባለው ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በቱርክ...
17/02/2026

የቱርክዬው "ቶግ" (Togg) የኤሌክትሪክ መኪና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በስጦታ ተበረከተ

የቱርክዬው ፕሬዝዳንት ረጀብ ጠይብ ኤርዶዋን በኢትዮጵያ እያደረጉት ባለው ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በቱርክዬ የቴክኖሎጂ ዕድገት ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተውንና የሀገሪቱ ኩራት የሆነውን "ቶግ" (Togg) የኤሌክትሪክ መኪና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በስጦታ አበርክተዋል።

ይህ ስጦታ ከመኪናነቱ ባለፈ በኢትዮጵያና በቱርክዬ መካከል ያለውን የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ቴክኖሎጂና ወደ ዘመናዊ ኢንዱስትሪ አጋርነት ማደጉን የሚያሳይ ትልቅ ምሳሌ ተደርጎ ተወስዷል።

ስጦታ የተበረከተው መኪና ዝም ብሎ ተራ ተሽከርካሪ ሳይሆን ቱርክዬ በዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ መኪና ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ያመረተችው የመጀመሪያው ሀገር በቀል ዘመናዊ መኪና ነው።

መኪናው ሙሉ በሙሉ በቱርክዬ መሐንዲሶች የተቀረጸና የተገነባ ሲሆን የቱርክዬን የኢንዱስትሪ ብቃት ለዓለም ያስተዋወቀ ፕሮጀክት ነው።

ቶግንከመኪናነት ባለፈ እንደ ተንቀሳቃሽ ስማርት መሣሪያ (Smart Device) ነው የሚታየው የላቀ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂና የኢንተርኔት ግንኙነት ሥርዓት የተገጠመለት ነው።

ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሠራ በመሆኑ ልክ እንደ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማትንና የታዳሽ ኃይል አጠቃቀምን ለሚያበረታቱ ሀገራት ተመራጭ ያደርገዋል።

የመኪናው ውጫዊ ገጽታ የቱርክዬን ባሕላዊ ቅርሶች (ለምሳሌ የቱሊፕ አበባን) ከዘመናዊ ምቾት ጋር አጣምሮ የያዘ ውበት አለው።

ፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ይህንን መኪና ለወዳጅ ሀገራት መሪዎች በስጦታ መስጠታቸው የቱርክዬን የቴክኖሎጂ አጋርነት ፍላጎት ያሳያል።

ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በስኬት በማከናወን ተመራጭ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ከተማ መሆኗን ያረጋገጠችው አዲስ አበባ
19/12/2025

ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በስኬት በማከናወን ተመራጭ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ከተማ መሆኗን ያረጋገጠችው አዲስ አበባ

14/12/2025
National Geographic's
12/09/2025

National Geographic's

09/09/2025
የድሮን ትርዒት በጉባ ሰማይ ላይ
08/09/2025

የድሮን ትርዒት በጉባ ሰማይ ላይ

Address

ሂጣታ
Awassa

Telephone

+251919540760

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alte pictures posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alte pictures:

Share

Category